ተስቲ ትሬዲንግ ያሰራው ትምህት ቤት ተመረቀ CURRENT By Admin Last updated Aug 21, 2018 0 704 Share Get real time updates directly on you device, subscribe now. Subscribe በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በቡና ኢንቨስትመንት ላይ የተሰማራው ተስቲ ትሬዲንግ የተባለው ሃገር በቀል ኩባንያ በራሱ ተነሳሽነት ከግማሽ ሚሊዮን ብር ወጪ በማድረግ በጉጂ ዞን ፡ ሻኪሶ ወረዳ ወስጥ ደንቢ ኦዶ በተባለ አከባቢ የኣንደኛ ደረጀ ት/ቤት ኣሰርቶ ኣባገዳዎች፡ባለስልጣናትና ህዝብ በተገኘበት በከፍተኛ ድሞቀት ኣሰመርቆ ቁልፉን ለህዝብ ኣስረከበ የት/ቤቱ መሠራት በኣከባቢው የነበረውን ከፍተኛ የመማሪያ ክፍል ችግር በመሰረቱ የሚፈታ መሆኑን ህዝቡና ኣባገዳዎች ገልፀው ከፍተኛ ምስጋናና ኣድናቆታቸውን ገልፀዋል ከዚህ በተጨማሪ የተስቲ ባለቤትና ስራ ኣስኪያጅ የሆኑት ኣቶ ፋይሰል ኣብዶሽ ዮኒስ ይህንን ህዝባዊ ወገንተኝነታቸውን ኣጠናክረው ለመቀጠልና በሚቀጥለው ዓመት በአከባቢው ተጨማሪ ክሊኒክና የውሃ ፓንፕ ገንብቶ ለህዝቡ በማስረከብ የህዝቡን ማህበረ ኢኮኖሚያዊ ችግር ለመፍታት የተቻለውን ሁሉ ለማድረግ ቃል የገቡ ሲሆን የኣከባቢው ኣባገዳዎች፡ኣመራሮችና ህዝቡም ኣስፈላጊው ድጋፍና ሙሉ ትብብር አንደሚያደርጉ በምረቃው ስነስርዓት ላይ ኣረጋግጠዋል፡፡ Admin See author's posts Share this:TweetTelegramEmailWhatsAppPrintShare on Tumblr Related 0 704 Share